ስልጠና ለመጠየቅ ይደውሉልን
+251 911-550-523
ስለ ሚፈልጉት ስልጠና በቀጥታ ያነጋግሩን።
ይህ ፕሮግራም በእናቶች ጤና፣ በቅድመ ወሊድ ፣ ድህረ-ወለድ እንክብካቤ እና በልጆች እድገት ላይ ጥልቀት ያለው ስልጠና ይሰጣል፡፡ በጣም አስፈላጊ በሆነው ጉዟቸው እናቶችንና ልጆችን የመደገፍ ችሎታ ያግኙ።
የሞግዚት ስልጠና እና የአፀደ ሕፃናት አያያዝ ፕሮግራም ህፃናትን በአግባቡ ለመንከባከብ፣ የዕድገት ደረጃቸውን ለመረዳት እና ለልጆች ደህንነትና ጤናማ እድገት የሚያስፈልጉ መሰረታዊ እውቀቶችንና ተግባራዊ ክህሎቶችን ለማስተማር የተዘጋጀ ነው።
ስልጠናው የህፃናት እንክብካቤን፣ የዕለት ተዕለት አያያዝን፣ የንፅህና እና ደህንነት አጠባበቅን፣ ከህፃናት ጋር ተገቢ የሆነ ግንኙነትን እና ለልጆች የሚስማሙ የመጫወቻና የመማሪያ እንቅስቃሴዎችን በመሰረታዊ ደረጃ ያካትታል።
በተጨማሪም ከወላጆች እና ከልጆች ጋር በኃላፊነትና በሙያዊ መንገድ መስራት የሚያስችሉ የግንኙነት ክህሎቶችን ያዳብራሉ።
ህፃናትን መንከባከብ እና የእድገታቸውን ጉዞ መደገፍ የሚፈልጉ ሁሉ ይህንን ስልጠና በመከታተል ተግባራዊ ክህሎት ማግኘት እና ለሙያዊ የሥራ እድል ራሳቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ።